Jimma University Open access Institutional Repository

የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የተከታታይ ምዘና አተገባበር ዳሰሳ በጅማ ከተማ በመንግስት ትምህርት ቤቶች ከ5ኛ-8ኛ ክፍል ተተኳሪነት

Show simple item record

dc.contributor.author ስመኝ አየለ
dc.contributor.author ጥበቡ ሽቴ
dc.date.accessioned 2022-02-17T11:27:39Z
dc.date.available 2022-02-17T11:27:39Z
dc.date.issued 2014
dc.identifier.uri https://repository.ju.edu.et//handle/123456789/6354
dc.description.abstract የተከታታይ ምዘናን መጠቀም የመማር ማስተማር ሂደትን ውጤታማ እንደሚያደርግ ይታመናል። በመሆኑም ይህ ጥናታዊ ጽሁፍ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ተከታታይ ምዘና አተገባበር ሂደት ፍተሻ ላይ ያተኮረ ነው። የጥናቱ ዋና ዓላማ በ1ኛ ደረጃ ከ5ኛ-8ኛ ክፍል በመንግስት ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የተከታታይ ምዘና አተገባበር ሂደት ምን እንደሚመስል መፈተሽ ነው። ጥናቱ ገላጭ የዳሰሳ ዘዴን (Descriptive Survay Method) የተከተለ ሲሆን መምህራንና ተማሪዎች መረጃ በመሰጠት በጥናቱ ተካተዋል። መረጃ ለመሰብሰብ ምልከታ፣ የጽሁፍ መጠይቅ፣ ቃለ መጠይቅ እና ሰነድ ፍተሻ ጥቅም ላይ ውለዋል። መረጃዎቹም በመጠናዊና በአይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ተተንትነው በመቶኛ፣ በሰንጠረዥና በገለጻ ቀርበዋል። የጥናቱ ውጤት የሚያሳየው የተከታታይ ምዘና ስልቶችን አብዛኛው መምህራን (75.6%) ሁልጊዜ፤ ጥቂቶቹ (9.6%) ደግሞ አልፎ አልፎ እንድሚተገብሩ ነው። በሌላ በኩል አብዛኞቹ ተማሪዎች (75.05%) መምህራኑ የተከታታይ ምዘና ስልቶችን በስራ ላይ የሚያውሉት አልፎ አልፎ እንደሆነ የገለጹ ሲሆን፤ የተቀሩት (24.48%) ደግሞ ሁልጊዜ እንደሚተገብሩት ገልጿል። በአጠቃላይ የጥናቱ ውጤት የሚያመለክተው የተከታታይ ምዘና ስልቶች ሙሉ በሙሉ እየተተገበሩ ነው ለማለት አያአስደፍርም። የጅማ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የተከታታይ ምዘናን አተገባበር ውጤታማ ለማድረግ ለመምህራን ተከታታይ ስልጠና መስጠት፣ በቂ የክፍለ ጊዜ ድልደላ ማድረግ፣ አስፈላጊውን የትምህርት መርጃ መሳሪያ ማሟላት እና የተከታታይ ምዘናው በዕቅድ እንዲመራ በማድረግ ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚያስችል የመፍትሄ ሃሳብ ተሰጥቷል። en_US
dc.language.iso en_US en_US
dc.title የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የተከታታይ ምዘና አተገባበር ዳሰሳ በጅማ ከተማ በመንግስት ትምህርት ቤቶች ከ5ኛ-8ኛ ክፍል ተተኳሪነት en_US
dc.type Thesis en_US


Files in this item

This item appears in the following Collection(s)

Show simple item record

Search IR


Browse

My Account