Jimma University Open access Institutional Repository

የሰዋስው ይዘቶችን በአሳታፊ ዘዴ ማስተማር የተማሪዎችን የሰዋስው ችሎታ እና የመጻፍ ክሂል ለማሳደግ ያለው ሚና

Show simple item record

dc.contributor.author ነኢማ ኑሩ
dc.contributor.author ማንያለው አባተ
dc.contributor.author ምህረት ሳዳሞ
dc.date.accessioned 2023-11-13T08:17:12Z
dc.date.available 2023-11-13T08:17:12Z
dc.date.issued 2015
dc.identifier.uri https://repository.ju.edu.et//handle/123456789/8842
dc.description.abstract ይህ ጥናት ያተኮረው የሰዋስው ይዘቶችን በአሳታፊ ዘዴ ማስተማር የተማሪዎችን የሰዋስው እውቀት እና የመጻፍ ክሂል ችሎታ ለማሳደግ ያለው ሚና ፍተሻ ላይ ነው፡፡ የጥናቱ ተተኳሪዎች በአመቺ የናሙና ዘዴ የተመረጡት በጅማ ዞን በሲግሞ ወረዳ የአዱ ሲግሞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ ጥናቱ ሙከራዊ የምርምር ንድፍን ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን፣ በተመረጠዉ ትምህርት ቤት በ2015 ዓ.ም ካሉ ሰባት የ10ኛ ክፍሎች መካከል በቀላል እጣ የናሙና ስልት የ10ኛ B እና 10ኛ E ክፍል ተማሪዎች የጥናቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ ቀጥሎም በእጣ መሰረት 10ኛ B የቁጥጥር ቡድን 10ኛ E ክፍል ደግሞ የሙከራ ቡድን መስርተዋል፡፡ በተጠኚዎቹ መካከል የስዋስው ትምህርትና የመጻፍ ክሂል ቅድመ-ግንዛቤ በጥናቱ ውጤት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተጽእኖ ለመከላከል ሲባል በተጠኚዎቹ አንጻራዊ ተቀራራቢ የሰዋስውና አንቀጽ መጻፍ ችሎታ ላይ መመርኮዝ አስፈላጊ በመሆኑ ቅድመ ትምህርት የሰዋስው እና አንቀጽ መጻፍ ፈተና ተሰጥቷቸዉ አንጻራዊ ተቀራራቢ ውጤት ያመጡት 40 /አርባ/ ተማሪዎች የቁጥጥርና የሙከራ ቡድኑ ተተኳሪዎች ተደርገዋል፡፡ ለዚህ ጥናት የመረጃ ምንጭ ሆኖ ያገለገለዉ የሰዋስው እና አንቀጽ መጻፍ ፈተናዎች ናቸው፡፡ ይህም ሰዋስውን በአሳታፊ ዘዴ ማስተማር በተጠኚዎቹ የሰዋስው ግንዘቤና የመጻፍ ክሂል ችሎታ ላይ ያስከተለውን ለውጥ ለመገምገም ጠቅሟል፡፡ የጥናት ውጤቱ እንዳመለከተውም ሰዋስውን በአሳታፊ ማስተማሪያ ዘዴ ድጋፍ የተማሩት የሙከራው ቡድን ተጠኚዎች ስዋስውን በ10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መጽሐፍ በቀረቡ ትእዛዛት ማስተማሪያ ዘዴ ከተማሩት የቁጥጥሩ ቡድን ተጠኚዎች የስዋስው ግንዛቤና የመጻፍ ክሂል ችሎታ ጉልህ ልዩነት ያለው (ውጤቱ t= 6.624, df =39, p= .000) መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ p= .000 ከጉልህነት ደረጃ ቋሚ ፓራሜትራዊ እኩልታ ማንጸሪያ p<0.05 የሚያንስ መሆኑ ታውቋል፡፡ በዚህም ሰዋስዉን ከአሳታፊ ዘዴ ጋር በማቀናጀት ማስተማር ከልማዳዊው የስዋስው ማስተማሪያ ዘዴ የተሻለ በሚያደርጉት ተግባራት ላይ የተመሰረተ እና የተማሪዎችን የሰዋስው እውቀትና የመጻፍ ክሒል ለማሻሻል ጠቀሜታ ያለው መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ en_US
dc.language.iso en_US en_US
dc.title የሰዋስው ይዘቶችን በአሳታፊ ዘዴ ማስተማር የተማሪዎችን የሰዋስው ችሎታ እና የመጻፍ ክሂል ለማሳደግ ያለው ሚና en_US
dc.type Thesis en_US


Files in this item

This item appears in the following Collection(s)

Show simple item record

Search IR


Browse

My Account